Monday, August 24, 2009

The October relief we are waiting for

AD21:- Enkuan aderesachihu.

less than two months left for the week we are waiting for a fundamental relief. AD21 believes that there is plenty of jobs to be done yet. We read statements from different churches and associations. We have learnt that laities are doing their part in reaching the fathers (members of the Holy Synod) with the statements. And today, we read that a group has took the task of drafting an online petition. We are happy for that as it was one of the proposals forwarded by
AD21 almost a month ago. But, as we read in the blog, we afraid that the launching of the petition may take some time - which should not be actually. We wish and ask the group to move forward as fast as possible given the short period of time we are left with. So all is going well though not to the satisfaction of AD21. But still there two main bodies we are waiting to hear from: the so calld sidetegnaw synodos and the alem aqef ye meemnan hibret. The fathers who are in the other part of the island should come out and say, we are here to help the mother church if there come a true initiative to cure the house. They should say, the church should get the primary attention and care than the father x or y as both will pass as they come to this world. The once flowered EOTC Laity Council too should wake up.

AD21

3 comments:

Anonymous said...

ene yemtsafim hone yemawrat limd yelnim. yemlqs enj. bicha silemitisrut negr hulu amsegnalhu. ahun emasflgew endzh mroal yemset mengedm yemaysay new. kenad abat gara swoyay lmn agr bet yalu senbt tmhrt betoch yebetekrstyan chigr ayfetm bilew bichohu wode betekhnetu belwal. ena men yimeslachuhal.

Anonymous said...

ቅኔ፦ የነሐሴ ኪዳነ-ምሕረት

እንደ-ዓምና እና እንደኻች ዓምናው ያኽል በይኾንም (ዓምና እንጦጦ ነበርኹ)፤ ዘንድሮም ባልጠበቅኹት ኹኔታ የኪዳነ-ምሕረትን በዓል ስቡሕ ተብሎ ምልጣን ተመልጥኖ ሲከበር በማየቴ እጅግ ደስ ብሎኛል። እንዲያውም የዕለቱ ቅኔ ያንተ ነው ተብየ እኔው ራሴ እንዳቅሜ ለመቀኘት ተዘጋጅቸ ሳለ፤ በሙያም በዕድሜም የሚበልጡኝ መሪጌታ ድንገት በቅዳሴው ሰዓት ስለመጡ፤ ግብዣው ለርሳቸው ተሻግሮ እጅግ የሚጥም ቅኔያቸውን ሰምተናል፤ በተለይ “ክብር ይእቲ”ው ልዩ ነበር።

አኹን ወዲህ ብቅ እንድል ያደረገኝ ነገር፦ በበዓሉ ማግስት ከካህናት አባቶች ገራ ሰብሰብ ብለን ስንጨዋወት፤ እኔ ያሰበኹት ቅኔ ምን እንደነበር ለማወቅ የጓጓ አንድ ወንድም፦ “አንተስ ምን ልትል አስበኽ ኖሯል?” ብሎ ጠየቀኝና፦ ለ“ዕጣነ-ሞገሩ” የ“አሠረ-ንጉሥ” ክፍል ያሰብኹትን ልንገርኽ ብየ ስጀምር፤ “ሙሉውን፣ ሙሉውን” አለኝ። እኔም ዕጣነ-ሞገሩን ሙሉ በሙሉ አንድ ጊዜ እንደዘለቅኹለት (የተራ ተማሪ ቅኔ እንደመኾኑ ቶሎ ስለገባው) “ይኸንማ ለብዙኃኑ ማሰማት አለብኽ” ሲለኝ፤ “ለከርሞ?” አልኹት። “እንዴ፤ ለምን ዛሬውኑ ጽፈኽ በኢንተርኔት አትለቀውም?” አለኝ። እኔም መልሸ “እንዴት አድርጌ? በዚያውስ ላይ ‘ዕጣነ-ሞገር’ የሚደረስ በቤተክሲያን፤ ወይስ ወደ‘መወድስ’ ልለውጠው ይኾን…” ብየ ገና ሳልጨርስ “ኧረ እንዲኹ እንዳለ ጻፈው፤ ባይኾን ትርጕሙንም አስከትል” አለኝ። እናም እነሆ ጻፍኹት፦

ዕጣነ-ሞገር (ዘፍልሰታ)

አለበውክነ ድንግል እምድኅረ-ጸዊሮት መስቀለ
ጸቢተ-ዘሕይወት ባሕር ከመ-ተክህለ።
ትንሣኤ-መድኅን ቀላይ እንተ-አድምዐት ጸሊለ
እስከነ-አርያም ዘተለዐለ፤
ጸውዐታ ዮም አኮኑ አስራበ-ደጊሞት ቃለ
ለዘለኪ ቀላየ-ትንሣኤ ዘምልዕት ኀይለ (1)

(“አሠረ-ንጉሡ” ከዚህ በኋላ ያለው ነው)

ዘኢጠየቅነሰ ኵልነ ይእዜ ወዘንሴአል ድንግለ
ከመ-በይኔሁ ለምንት፤ እምድኅረ-ጸዊሮት ሰይለ
ጊዜ-ክልኤቱ፤ ተአንተለ
ኀይለ-ትንሣኤሃ ለእም፤ ወኢያብጠለ
ዘፍልሰታ ወሞታ ሰይቀለ።
ትርጕም፦
ድንግል ሆይ፦ መስቀል ከተሸከሙ ወዲያ
በሕይወት/ባሕር መዋኘት እንዲቻል አስረዳሽን።
ከፍ እስካለው አርያም ድረስ
መንሳፈፍን ቶሎ ያገኘች የመድኅን ልጅሽ ትንሣኤ/ቀላይ
ታምር የተመላች ያንችን ትንሣኤ/ቀላይ
ቃልን በመድገም/ፏፏቴ ዛሬ ጠርታታለችና።

(አሠረ-ንጉሥ)

አኹን ኹላችን ያልተረዳነው፤ ድንግልንም የምንጠይቀው ግን
በምን ምክንያት
በኹለቱ ጊዜ መከራ ከመሸከም በኋላ
የእናት (የኢትዮጵያ/የቤተክርስቲያን) የትንሣኤዋ ታምር ቸል እንዳለ፤
የፍልሰቷ (የመፍረሷ) እና የሞቷም እንዝርት/[ዘመን] (መሽከርከሩን፣ መመላለሱን) አላቋርጥ እንዳለ ነው።

(1) ጥቅስ:-

“ቀላይ ለቀላይ ትጼውዖ (ዓ) በቃለ-አስራቢከ” (በፏፏቴኽ ድምፅ ቀላይ ቀላይን ትጠራዋለች) መዝ ፵፩፥፯

ስሜ ይቆያችኹ ( “ለምን?” ብትሉኝ)፦

በቅኔው ንባብ ወይም በምስጢሩ አለያም ባገባቡ ስሕተት ቢገኝበት የማፍር፤ ወይ ደሞ ሊቃውንት ቢያርሙኝ አልታረምም በማለት የምገግም፤ ኾኜ አይደለም። እንዲህ ያለው አስተሳሰብ ከኔ ይራቅ። ነገሩ ወዲህ ነው።
ደሞ አንዱ “እም”ን ለሀገሪቱ ሰጥቶ፦ “ክልኤቱ”ን ደርግ እና ኢሕአዴግ፤ ወይም መለስ እና ኢሳይያስ ብሎ ቢገልጣቸውስ? አንድም “እም”ን ለቤተክርስቲያን ሰጥቶ “ክልኤቱ”ን አባ እገሌ እና አባ እንቶኔ አድርጎ ቢፈታቸውስ? እናንተም እሱን ተከትላችኹ በእሊህ ድንበር (ያገር/የቤተክሲያን ዕድር) አፍራሾች ዘመን ባገራችን እና በቤተክሲያናችን ላይ የወረደውን መከራ አንድባንድ እየዘረዘራችኹ፤ የመከራው እንዝርት ይሰበር ዘንድ፤ የራስን ጥረት እያደረጉ ድንግልን የሙጥኝ ማለት እንዲገባ በሚያሳስብ አኳዃን፤ ምስጢሩን ብታራቅቁትስ? ነገሩ በጥልቅ የሚያሳስባቸው ምእመናን ዕለቱን ባይኾን ውሎ አድሮ ቢያንስ ቢያንስ “እግዚኦታ አውጁልን” ሊሉ አይደለም? በርግጥ እንዲኽ ያለው ጥያቄ በምንም መሥፈርት (የሰውን ከፈጣሪው መቅረብ ከማይሻ ከሰይጣናዊ መሥፈርት በቀር) ክፉ አይደለም። ነገሥታቱም ኾኑ አባቶች ራሳቸው ጭምር የንስሐው ጸሎት ተሳታፊዎች--እንዲያውም ዋና ተነሳሕያን--ቢኾኑ እና እግዚኦታውን ቢያስፈጽሙት የሚከብሩበት፣ አገራችንን እና ቤተክሲያናችንንም የሚታደጉበት መኾኑን ባላጣውም፤ ይኸንን ለማድረግ ምን ያኽል ዝግጁ ናቸው? ይልቁን በተቃራኒው አያስቡም?
ድንገት በተቃራኒው ካሰቡ፤ ያኔ እኔ ወዴት እደርሳለኹ? “ኒንጃዎቹ” ያስቀምጡኛል ብላችኹ ነው? (አልዋሻችኹም፤ ካገሬ ከወጣኹ አንድ ዓመት ሊሞላኝ ምንም ያኽል አልቀረኝም። ነገር ግን እግዜር ፈቃዱ ኾኖ አሁን ካለኹበት ቦታ ሻል ያለ ነጻነት ወዳለበት አገር ኼጄ እንደ-ልቤ ለመንቀሳቀስ የሚያስችል የመታወቂያ ወረቀት ያገኘኹ እንደኾነ፤ ውድ ባለቤትን እና ልጆቸን ለማየት ወዳገሬ ለመመለስ ዐሳብ አለኝ።) ታዲያ ለናጅሬ ስሜን ከወዲሁ ካስታወቅዃቸው፤ ገና እግሬ ቦሌን ሲረግጥ፤ እንደ ታላላቆቹ ፖለቲከኞች፦ የመንግሥት ክህደት (“treason”) በሚል ሰበብ (technical charge) ባይኾን እንኳ፤ እንደወጣቶቹ፦ “ሰው ገጨ ነገር ቋጨ (ጠመዘዘ፣ አከረረ)” አሰኝተው ቃሊቲ አያስወረውሩኝም ይመስላችዃል? ለዚያ ደሞ የኔ ትከሻ ገና ነው።

azekiridingel said...

As Ato Nigussie of VOA has recently put it right, the Qene, as one of the golden legacy of the EOTC, used to play big role in conveying outrages and disappointments to the leaders of the Church and the country that they can fix their wrong doings. From the last anonym, AD21 has learnt that the instrument can also be used today. We appreciate. Good to post outrages one or the other way - October is coming.