Tuesday, July 28, 2009

Recapping my cries

Dear Orthodoxawuyan,
I read a good wake up call from our Deje Selam today. As I frequently said, we should use our time and empower the fathers that they, in October, can push the most important agenda they could somehow raised last month. We don't have to wait for a wind of gossips and reports to move like we all did last time. This is a time God gave us to intensify the good fight. Let us organize clergies, laities, sunday schools, organizations in our neighbourhoods to come together and stand firm against the evils of our church. When we do so, the fathers will be energized to push the agenda forward and reach at a decision which enable our mother church show us her true beauty. I still believe that the seven question I threw at the eyes of the fathers are not invalid. I paste them here too:

1. የዚህ ቅዱስ ጉባኤ አባላት /ብፁዐን አበው/ ከእንካ ሰላትያ ርቀው የቤተ ክርስቲያሩን ልጆች በሀፍረት አንገታችንን ያስደፉ ልቡናችንን ሲበዘብዙ የሚኖሩ መሠረታዊ ችግሮች ላይ ተወያይተው በመንፈሳዊ ሐሴት እግዚአብሔርን እንድናመሰግን እነሱንም እንድናከብራቸው የሚያደርጉ ውሳኔዎችን በጉጉት እንደምንጠብቅ እንዲረዱ፤ እንደ ተለመደው በኮሚቴ ይጠና ብላችሁ እንዳትቀብሩትና እንዳትቀብሩን፤

2. ሊቃነ ጳጳሳቱ ቤተ ክርስቲያናቸው ሥልጣኑን የሰጠቻቸው ከውስጣዊ ምዝበራና ከውጫዊ ውርወራ እንዲጠብቋት መኾኑን ተገንዝበው ያለምንም ፍርሐትና አድር ባይነት ቀረቡ በተባሉትም ኾነ እነሱ በየማስታወሻቸው በያዟቸው ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ችግሮች ዙሪያ እንዲከራከሩ

3. ጉባኤው በቤተ ክርስቲያሩ መሠረታዊ የአስተዳደር ችግሮች ላይ ተወያይቶ መፍትሔ ሲሰጥና ቤተ ክርስቲያሩ ተጠያቂነትንና ግልጽነትን ያረጋገጠ አስተዳደራዊ ስልት ስትዘረጋ የጥቅም ጉሮሮአችን ተዘጋ ብለው የሚጮኹ ውሾች በቤተ ክህነቱ ውድማ እንደሚኖሩ አውቀው እዚያ ወርቃማ ውሳኔ ላይ እንዳይደርሱ በግልጽና በስውር የሚያቀብሏቸውን የሐሳብ ተዋሕስያን ይዘው ወደ ተቀደሰው ጉባኤ እንዳይገቡ፤ የሽጉጥ ማስፈራሪያቸውንም ከቁብ እንዳይቆጥሩ፤

4. ውይይታቸውና ውሳኔያቸው ሁሉ የነገውን የቤተ ክርስቲያን ጉዞ የሚያስተካክል እንጂ የትላንትን ስሕተት የሚደግም ወይም ምክንያት የሚሰጥ እንዳይኾን፤

5. የአገሩ መንግሥት ከቤተ ክህነቱ ቅጽር ግቢ ተስፈንጥሮ ወደ ላይ ጉኖ ሲያበቃ የሚነጉደውን ዜና አልሰማም ማለት ጅልነት ስለሚኾን በግልጽም ይሁን በስውር በጉባኤው ላይ እጁን እንዳያሳርፍ፤ ለአባቶቻችን ነጻነት እንዲሰጥ፤

6. ምእመናን አሁን ያሉት ሊቃነ ጳጳሳት ያገለግሉን ዘንድ እግዚአብሔር የሾመልን አገልጋዮቻችን እንጂ የቤተ ክርስቲያሩ ባለቤቶች እኛ መኾናችንን ተረድተን ጉዳዩን በጥንቃቄ እንድንከታተለውና ነገ እናገኘው ዘንድ ለምንፈልገው የእናት ቤተ ክርስቲያናችን ሙቀት እውንነት አባቶቻችን በጥንካሬ ተወያይተውና ተከራክረው ጠቃሚ ውሳኔ ላይ እንዲደርሱ በያለንበት ግፊት እንድናደርግ፤

7. የቤተ ክርስቲያሩን የነገ ጉዞ የተቃና እንዲኾን ከልብ የሚመኙና ለዚያም በትጋት የሚሠሩ ግለሰቦች፣ ድርጅቶችና ማኅበራት ቤተ ክርስቲያን ከተጣባት የአስተዳደር ደዌ የምትፈወስበት ጊዜው አሁን መኾኑን ተረድተው እውነት እንድታሸንፍ የቻሉትን ያህል እንዲያደርጉ፤
I believe that all will be answered in October. But I equally believe that unless we do our part, the fathers will neither answer the above listed questions nor fulfil our wishes. So let us do our part defining the problems from general to particular and propose points which we think can be solutions.
will continue..
AD21

1 comment:

Anonymous said...

well said sir/madam. hope my poor amaharic helped me to understand the seven questions you forwarded. we should distant ourselves from gossips and get focused on what we can do until October. I agree that we should organize our neighbors.